ብኢኮ በኢትዮጲያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት የተቋቋመና በኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራ ልማታዊ ተቋም ነው፡፡
ብ.ኢ.ኮ በርካታ የወታደራዊና የሲቪል ምርቶች ማምረቻ ፋሲሊቲዎችን በመገንባት የሀገራችንን የኢንዱስትሪ ልማት በማፋጠን ላይ የሚገኝ ተቋም ነው
ብኢኮ በርካታ የማኑፋክቸሪንግና የሃይል ማመንጫ ፕላንቶችን ከዲዛይን እስከ ግንባታና የምርት ሙከራ ያሉ ስራዎችን ያከናውናል፡፡ ዋና ዋናዎቹ ፕሮጄክቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
ኮርፖሬሽኑን ከገባበት ቀውስ ለማውጣት እየሠራ ያለው አዲሱ አመራር በፍጥነት ለማገገም ጠንካራ ክትትል እያደረገ ይገኛል። ኮርፖሬሽኑ በሪፎርም ዕቅዱ 4ግቦችን በማስቀመጥ ከኦፕሬሽናል ሥራው ጎን ለጎን በማስኬድ እየሠራ ይገኛል፡፡
ዋና ዳይሬክተር ብ/ ጄ አህመድ ሃምዛ የምርት ሂደቶችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን ኣመራርና ሰራተኞችንም አነጋግረዋል፡፡በኮርፖሬሽኑ ምን እየተሰራ እንዳለና አሁን ካለንበት ችግር ለመውጣት እንዴት የቀን የምርት መጠናችንን ማሻሻል እንችላለን የሚሉ ዋና ነጥቦች ላይም ውይይት ተደርጓል፡፡
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አመራሮች ከአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት ከተውጣጡ ሶስት ሺህ ወጣቶች ጋር ተወያዩ፡፡